የአብን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ስብሰባ ረግጠው ወጡ! (አሻራ ሚድያ)

የአብን የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት ስብሰባ ረግጠው ወጡ!

አሻራ ሚድያ


*…. በወለጋ_የተጨፈጨፉ_ከ2500 በላይ ደረሰ

ዛሬ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአብን አባላት ስብሰባውን አቋርጠው ወጥተዋል። ረግጠው የወጡበች ምክንያት በዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ አማካኝነት ቀዳሚ አጀንዳ ወለጋ ጊምቢ ስለተጨፈጨፉት ወገኖቻችን ብሄራዊ የሃዘን ቀን እንዲታወጅ፣ ስብሰባውም በህሊና ጸሎት እንዲጀመርና ጠቅላይ ሚኒስትሩም በም/ቤቱ ቀርበው በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እንዲሰጡ ለአፈ-ጉባኤው ቀርቦ እንደነበር እና ነገር ግን አፈ-ጉባኤው ግን አጀንዳው እንዲያዝ አልመፍቀዳቸው ታውቋል።

በዘር-ተኮር በሆነው ጭፍጨፋ ከ400 በላይ ዜጎቻችንን ባጣንበት ወቅት ስብሰባውን እንደ አዘቦት ቀን መታደም ለህሊናችን ስለከበደን የሚከተሉት የአብን አባላት የም/ቤቱን ጉባኤ አቋርጠን ለመውጣት እንደተገደዱ ከዚህ በታች ያሉ የምክር ቤት አባላት መረጃውን አድርሰውኛል።

1. ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ (የባህር ዳር ተወካይ)

2. አቶ አበባው ደሳለው (የጅጋ /ምዕራብ ጎጃም ተወካይ)

3. አቶ ሙሉቀን አሰፋ (የሸበል በረንታ- ዕድ ውሃ ተወካይ)

4.አቶ ዘመነ ሃይሉ (የጭስ አባይ ተወካይ)

መረጃ ያደረሱኝ የምክር ቤት አባሉ አክለውም አቶ ክርስቲያን ታደለ የቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ስለሆኑና የሳቸው ኮሚቴ ሪፖርት ስለሚያቀርብ ስብሰባውን አቋርጠው መውጣት እንዳልቻሉም ገልጸውልኛል።

ሙሉጌታ አምበርብር

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.