” ቶሎ አገራችንን ልቀቁ አለበለዚያ እርምጃ እንወስዳለን” እየተባልን ነው ለወገን አድርሱልን…!!!
-በቄለም ወለጋ ዞን በሰዮ ወረዳ በደቢዶሎ ያሉ አማሮች
ሮሐ ኒውስ
በቄለም ወለጋ ዞን በሰዮ ወረዳ #በደቢዶሎ ከተማ 04ቀበሌ ውስጥ የሚኖሩትን አማራወች በ4/11/2014 ከምሺቱ 3ሰአት ጀምረው ኦነ*ግ ሼ*ኔወች በየቤታቸው በመዞር የባንክ አካውታችሑን አምጡ : በተቀረ ትገ*ደላላችሁ : ምን እየሰራችሁ ነው ወደአገራችሁ ግቡ : ሐገሩ የኛንጅ የእናንተ አይደለም : ንብረት መሸጥ መለወጥም አትችሉም : ስለዚህ እርምጃ ከምንወስ*ድባችሑ በፊት ልቀቁ በማለት ሲያሰ*ቃዩዋቸው ማደራቸውን ምንጫችን ከስፍራው አድርሶናል::
በአለም ላይ ያላችሑ ሁ አማራወች ድምጽ ሑኑን : ወደሐገራችን መግባትም አልቻልንም : ሕይወታችንን ታደጉልን ብለዋል::
#ሌላው
በደቢዶሎ ዙሪያ ያሉ ቀበሌወች : በሰዮ ወረዳ ውስጥ #በቀልቀልቻ_ቡቡካ_ቀበሌ ገላኖ : ሜጢ : ወልገይ : ጉዲና : እሪጳ : አየር ማረፊያ : ጉቴ ሰዮማ በሚባሉ ቀበሌዎች ውስጥ ያሉ አማራወች ዘንድ እየገቡ በግ*ዴታ ምግብ ይመገባሉ : ከተመገቡ በኃላ ወደሐገራችሑ ለምን አትመለሱም : ይሔ የእናንተ ሐገር አይደለም አንድቀን እርምጃ እንወስድ*ባችሑለን : መንግስት እሚለውን አትስሙ በማለት እያ*ሰቃዩአቸው እንደሖነ መረጃ አድርሰውናል::
የመንግስት የጸጥታ አካልም በአካባቢው የሉም : ከተማ ውስጥ ቢኖሩም ምንም አይነት እር*ምጃ እየወሰዱ እንዳልሆነና ብናመለከትም እሚሰማን የለም : አርፋችሁ ተቀመጡ የሚል ምላሺ ነው የተሰጠን ብለዋል::