>

የኦሮሞ ወረራ ምልክቱ ከተማ አውዳሚነቱ (ጌጥዬ ያለው)

የኦሮሞ ወረራ ምልክቱ ከተማ አውዳሚነቱ

ጌጥዬ ያለው
የኦሮሞወረራ ከሩቅ ከሚለይባቸው ምልክቶቱ መካከል አንዱ ከተማ አውዳሚነቱ ነው። በአራት አመታት ውስጥ ኤፊሶንን አውድሟል፣ ሻሸመኔ እና ዝዋይንም አቃጥሏል። እነኚህ የእጅ መፍቻዎቹ ናቸው። ትልቁ ህልሙ የአማሮቹ፤ የእነ አጼ ዳዊት የእጅ ሥራ አዲስ አበባ ነች።
ይቺ ከተማ ማለትም የያንጊዜዋ #በራራ በ16ኛ መቶ ክፍለ ዘመን በኦሮሞ ወረራ (የግራኝ አስተዋፅኦ ሳይረሳ) ፈርሳለች። ከዓመታት በኋላ #እምዬምኒልክ መልሰው አደሷት። እነሆ አሁንም ወራሪዎች አንዣበውባታል፤ እንደገና ልትፈርስ ነው። መቼም የኢትዮጵያ ታሪክ በጥቅሉ ከተነበበ የሐቅ መስመሮቹ የሚታዩት አማራ ሲገባ ኦሮሞ ሲያፈርስ ነው።
ኦሕዴድ ወደ ሥልጣን እንደመጣ ቀዳሚ አጀንዳው ያደረገው አዲስ አበባን ነው። የለውጥ ተብየው ጭብጨባ ገና ሳይረግብ የኦሮሞ ፓርቲዎች ቡድን በጋራ በኢለሌ ሆቴል በሰጠው መግጫ እንዲህ አለ፦
. . . አዲስ አበባ በታሪክ፣ በስነ ልቦና፣ በሕግ የኦሮሞ ብቻ ነች። ሌላው ጅማና ነቀምቴ እንደሚኖረው መኖር ይችላል. . .
ሕጉን ለጊዜው እናቆየውና የከተማዋን ታሪክና ስነ ልቦና በጥቂቱ እንይ፦ በታሪክ አዲስ አበባ የኦሮሞ ልትሆን ቀርቶ፤ #በአጼዳዊት ስትቆረቆር ኦሮሞ ወደ ኢትዮጵያ አልተሰደደም ነበር። በኢትዮጵያ ውስጥ አልነበረም። ዳግማዊ ምኒልክ እንደገና ሲያድሷትም ድንጋይ አላቀበለም። ከተማዋን ከእነርሱ ይልቅ በወቅቱ በዳግማዊ ምኒልክ ተቀጥረው ድንጋይ ያቀብሉ የነበሩ ነጮች የተሻለ ያውቋታል።
በስነ ልቦና ከተመዘነም እንኳን መላው አዲስ አበባ ስታዲዮም የሚገኘው የኦሮሞ ባሕል ማዕከልም የኦሮሞ አይደለም። ውስጡ ስንገባ የተቆረጠ የወንድ ብልት ምልክት ግንባሩ ላይ ከለጠፈው ሰው ምስል ውጭ በአመዛኙ የአማራ ባሕል ነው በስርቆት የተቀመጠበት። ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከእነ ቀለም ምርጫቸው የተኮረጁ ስዕላት፣ የአማራ አልባሳትና የሙዚቃ መሳሪያዎች በጥቂቱ ይጠቀሳሉ። ከተማዋ የኦሮሞ ስነ ልቦና እንደሌላት ኦነግ አስፋልቱን ሁሉ እስከ ዊንጌት አደባባይ እየቀባ ሆ! ብሎ ሲገባ፤ ሆ! ብላ መልሳ አሳይታለች። ፒያሳ ላይ የዱላ ክትክት አድርጋ መልሳለች። በዚህ ጊዜ በአስለቃሽ ጭስ እስኪበተን ድረስ የአዲስ አበባ ወጣት መንግሥታዊ ድጋፍ ያለውን የኦነግ ግሪሳ ፒያሳ ላይ አንገት ለአንገት ሲተናነቅ መሀሉ ውስጥ ቆሜ አይቻለሁ። እንዲህ የተናነቀው ያለ ማንም አደራጅ፣ ያለ አንዳች የጦር መሳሪያ ነበር። ባልደራስ ቀሰቀሰው እንዳይባል ገና እንደ ባለአደራ ምክር ቤትም ሆነ እንደ ፓርቲ አልተመሰረተም ነበር።
ግሪሳው የሀጫሉ ሁንዴሳን ግድያ ተከትሎ አዲስ አበባ ሲገባ እንዴት እንደተመለሰም የሚዘነጋው አይመስለኝም። በቅርቡ በአዲስ አበባ የመንግሥት ትምህርት ቤቶች በግድ ኦሮምኛ ለማስዘመር እና የገዳን ጨርቅ ለማውለብለብ የሞከሩ ኦሮሞ መምህራን በተማሪዎቻቸው እስከ መደብደብ ደርሰዋል።  ከተማዋ የኦሮሞ ስነ ልቦና ቢኖራት ኖሮ ይህ ሁሉ ባልሆነ ነበር።
ኦሕዴድ በወኔ ስር ሆኖ ባጠናው ጥናት መሰረት አዲስ አበባ የሚኖረው የኦሮሞ ተወላጅ 19 ከመቶ ነው። 61 ከመቶው አማራ ነው። ሌሎቹ 20 ከመቶውን ይይዛሉ። እዚህ ላይ አንድም ስላተቆጠሩ ሌላም ማንነታቸውን ተነጥቀው በኦሮሞነት ስለተቆጠሩ ነው እንጂ ከአማራ ቀጥሎ ከፍተኛውን ቁጥር የሚይዙት ቤተ ጉራጌዎች ናቸው የሚሉ ትንታኔዎችም አሉ።
ሌላው ልብ ሊባል የሚገባው ጉዳይ አለ የተባለው 19 በመቶ ኦሮሞ እንኳን እነርሱ የኦሮሞ ስነ ልቦና የሚሉትን የኦነግ እከክ የተሸከመ አይደለም። እንሌላው ኗሪ የከተሜ ስነ ልቦና ያለው ነው።
የከተማዋን የሕዝብ ስብጥር ለመቀየር የሞቀ እንቅስቃሴ የተጀመረውም በታከለ ኡማ መሪነት የመንግሥት ሠራተኞች የብሔር ስብጥር ተጠንቶ ከ70 በመቶ በላዩ አማራ መሆኑ ከተረጋገጠ በኋላ ነው። ከዚህ በኋላ ነው የሲቪል ሰርቪስ አዋጁን ጥሰው ኦሮሞ ብቻ መቅጠር፣ ሕገ ወጥ የኗሪነት መታወቂያ መናኘት የጀመሩት።
ይህም ሆኖ አዲስ አበባ ፊንፊኔ መሆን አልቻለችም። አትሆንምም!
Filed in: Amharic