>

ሴትነት በገዳ የደም ማህበር ውስጥ (ጌጥዬ ያለው)

ሴትነት በገዳ የደም ማህበር ውስጥ

ጌጥዬ ያለው


ብዙ ጊዜ “የገዳ ስርዓት“ እየተባለ ይነገራል፤ ይፃፋልም። በፕሮፖጋንዳ ድግግሞሽ የመጣ ኢ-ሳይንሳዊ የሀሰት ተረክ ነው። ገዳ ለአቅመ ስርዓትነት አልደረሰም። በትክክል ይጠራ ከተባለ የደም ማህበር ነው። ታዲታ በዚህ ማህበር ውስጥ ሴትነት እንዴት ነው የምትታየው?

፩. በገዳ የደም ማህበር ውስጥ ሴቶች የተናቁ እና የተገለገሉ ናቸው። የመሪነት፣ የዳኝነትም ሆነ የጦር ተሳታፊነት ሚና መፈፅሞ የላቸውም። በማህበሩ ደንብ መሰረት አንድ #ኦሮሞ ተገርዞ የገዳ መሪ በሆነባቸው ሁለት አመታት ውስጥ ሴት ከወለደ ወደ ጓሮ ወስዶ ጨቅላዋን አርዶ እንዲገድላት ይገደዳል። ወንድ ከወለደ ግን ያሳድገዋል። ከሁለት አመቱ በኋላ ከተወለደች የወንዱን ያህል ፍቅር ባታገኝም ሴቷም ታድጋለች።

፪. ሴት በአባትዋ ቤት ከወንድሞቿ ጋር ርስት ወይም ውርስ መካፈል አይፈቀድላትም።

፫. አባት ሴት ልጁን ሲድር “ልጀን ሽጫለሁ” እንጂ “ድሬያለሁ” አይልም። ባሏም እንደ ባርያ ቀጥቅጦ ይገዛት ዘንድ ተፈቅዶለታል። ኮብልላ ሄዳ ሳትዳር (በገዳ አባባል ሳትሸጥ) ብትወልድ ልጇን ጨምሮ በግዳጅ ወስዶ ቀጥቅጦ ይገዛታል።

፬. በሰው ብትገደል የነፍስ ዋጋዋ ከወንድ በግማሽ ያነሰ ነው። (የወንዱ ዋጋ መቶ ቁም ከብት መሆኑን ልብ ይሏል) የነፍስ ዋጋ እንዲህ በመመሪያ ተተምኖ የቀረበው ግድያ የዘወትር ተግባር ስለሆነ ነው። ምክንያቱም ወንድ ያልገደለ አያገባም፣ ቅማል ሲመጠምጠው ይኖራል እንጂ ፀጉሩንም አይላጭም። ስለዚህ ስጋዊ ፍትሆቱን ለመፈፀም እና ለመላጨት ሲል የሩቅ ሰው ቢያጣ ወንድሙን ይገድላል። ሴቶች ያፈቀሩትን ገና ከሴት ያልደረሰ ጎረምሳ ለማግኘት ሲሉ ወንድማቸውን፣ ልጃቸውን፣ አባታቸውን ጊዜ እና ቦታ አመቻቸተው ያሰገድላሉ። ልብሳቸውን በፍየል ደም አጨማልቀው መጥተው “እዚያ ማዶ ሰው ገደልኩ፤ ነገር ግን ቆርጨ የያዝኩትን ብልቱን ዘመዶቹ ከበው ነጠቁኝ” እያሉ በሀሰት የሚያገቡና የሚላጩ የኦሮሞ ወንዶችም በርካታ  ናቸው። ወራሪው የኦሮሞ አገዛዝ ይህንን ልማድ ነው ለመመለስ እየሞከረ ያለው።

፭. ሴት በባሏ ላይ ስትማግጥ ብትያዝ ከሁለቱም ወንዶች ጋር የባልና ሚስት ያህል ግንኙነት እያደረገች መቀጠል ብልግና መለያው የሆነው የገዳ ማህበር ያረጋገጠላት መብቷ ነው።

ውሽማዋ ግን ለባሏ የቅናት ዋጋ አንድ ወይፈን ይከፍላል። በተረፈ ሁለቱ ወንዶቿ እየተፈራረቁ ሲገናኟት በር ላይ ለምልክት ጦር ተክለው በመግባት ነው። ጦሩ ተተክሎ ከሆነ ሚስተየዋ ከሌላኛው ባሏ ጋር ነች ማለት ነው፤ ስለዚህ አንደኛው ድንገት ከደረሰ በደጅ ሲንጎራደድ ወይም ከጎረቤት ጋር ሲጫዎት ይቆያል እንጂ ውሽማዋ ሳይወጣ አይገባም።

ይህንን ድንቁርና ነው ስርዓት ገለመሌ እያሉ ለኢትዮጵያውያን ሁሉ ለመናኘት እየሰሩ ያሉት።

Filed in: Amharic