>

የጦርነትም የሰላምም ዕዳ ከፋዮች ሆነን እስከመቼ  (ቴዎድሮስ ሀይለማርያም)

የጦርነትም የሰላምም ዕዳ ከፋዮች ሆነን እስከመቼ ❓

ቴዎድሮስ ሀይለማርያም


   1. በተደጋጋሚ ተክደናል ‼️ ሆድ ይፍጀው ብለን ትተነው  እንጂ ብልፅግና ባለፉት ሶስት የትግራይ ወረራዎች ወቅት  በተደጋጋሚ ያለሀፍረት ክዶናል።  በጦርነቱ ሂደት በህልውና ዘመቻው  የተሰለፈውን ኃይላችንን በግንባርም  ከጀርባውም  እያሴረ ፣ በሰሜን ስንፋለም በደቡብ ወገናችንን እያስጨፈጨፈ የጅብ ወዳጅ ሆኖብናል።  ጦርነቱ በአስተማማኝ ድል እንዳይቋጭ በማሴር  የህዝባችንን መስዋዕትነት ከንቱ አድርጎብናል።

2. ከምር ተንቀናል ‼️ ወያኔ/ትህነግ በተፈጥሮውም ፣ በርዕዮቱም ፣ በግብሩም የአማራ  ደማዊ ጠላት ነው፡፡  ሆኖም የብልፅግናን ያክል ምራቁን  የተፋብን የለም። መሪዎቻችንን ፣ ጀግኖቻችንን ፣ አንቂዎቻችንን እየገደለና እያጋዘ  ፣ ተቋማቶቻችንን በምንደኞች  እያሰረገና እያፈረሰ ፣ ህዝባችንን እየከፋፈለና እያባላ እግር ተወርች አስሮናል።  የትግሬ ወራሪ  ሲዳከም እየደገፈ  ፣  ኦነግ/ሸኔን በገፍ እያሰለጠነና እያስታጠቀ  እረፍት ነስቶናል።

   3. አሁንም ከጀርባ ተወግተናል ‼️  የሰላም ድርድሩ አያገባችሁም ፣ ከልቅሶ በላይ  ምንም አታመጡም  ተብለናል፡፡  ሰላሳ ዓመት በፈረቃ ሲያጠቁን የነበሩት አማራ ጠሎች  እየተደራደሩብን ፣ የወገኖቻችን እንባና ደም ሳይደርቅ   በገሀድ እንደገና እየተቃቀፉብን ነው። ህዝባችን የጦርነትም  የሰላምም  ብቸኛው ዕዳ ከፋይ እንዲሆን ተፈርዶበታል። በምንም መንገድ  እርቃናችንን ልናለባብሰው አንችልም ። ዝምታውን ሰብረን  እንደ ህዝብ አስቸኳይ መፍትሔ መፈለግ አለብን።

Filed in: Amharic