>
5:13 pm - Sunday April 19, 4195

ዶ/ር ደብረፅዮን በምክትል ጠ/ሚነት  ሊሾሙ ነው...! (ተራራ ኔትዎርክ - ታምራት ነገራ)

ዶ/ር ደብረፅዮን በምክትል ጠ/ሚነት  ሊሾሙ ነው…!

    ተራራ ኔትዎርክ – ታምራት ነገራ


የህወሓት ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል የኢትዮጲያ ምክትል ጠሚነት ሹመት ሊሰጣቸው መሆኑን የተራራ ኔትዎርክ ምንጮች ጠቁምዋል፡፡   በሓወሃትና የፌደራል መንግስት መካክለ  በቅረቡ የተደረገውን ስምምነት መሰረት ባደረገ መልኩ አዲሰ የካቢኔ ድልድል አንደሚኖር የጠቆሙት ምንጮቻችን በርካታ የህወሃት ፖለቲካዊና ወታደራዊ ባለስልጣናትን ወደፌደራል  ስልጣኖቸና በከፍተኛ ማዕረግ ወደ መከላከያ መልሶ ለማካትት ቅድመ ዝግጅት እየትገባደደ መሆኑን ለተራራ ኔትዎርክ ገልጰዋል፡፡

 

ከነዚህ ባለስልጣናትም መካክል ግንባር ቀደምትነቱን የሚውስደው ዜና የዶ/ር ደብረፅዮን ለምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴርነት መታጨት ሲሆን በመቀጠል ደግሞ አቶ ጌታቸው ረዳን ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ለመሾም አንደታቀደ ለማወቅ ተችሏል:: አቶ ጌታቸው ረዳ የውጭጉዳይ ሚኒስቴር ካልሆኑ ደግሞ  የጠ/ሚኒስትር አቢይ የውጭ ጉዳይና ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ ሆነው ሊሾሙ አንደሚችሉና በአሁን ወቅት የውጭ ጉዳይና ብሄራዊ ደህንነት አማካሪ የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ሊሾሙ እንደሚችል ምንጮቻችን ምልከታቸውን ሰጥተዋል፡፡

 

    በአሁኑ ወቅት የምክትል ጠ/ሚነቱንና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርንቱን ደርብው የያዙት አቶ ደመቀ መኮንን በአዲሱ የሰልጣን ሽግግር ኒውዮርክ በሚግኘው የተባባሩት መንግስታት ጵሀፈ ትቤት በሙሉ አምባሳደርነት ለምሾም እንደታቀደና ይህንንም ለማመቻችት አቶ ደመቀ የአምባሳደርነት ስልጠና እየወሰዱ እንደሰነበቱ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Filed in: Amharic