>
5:13 pm - Friday April 18, 6910

የጭራቅ አሕመድ ታንክ፤ የሽንፈቱ ምልክት (መስፍን አረጋ)

የጭራቅ አሕመድ ታንክ፤ የሽንፈቱ ምልክት 

“በመጀመርያ ይንቁሃል፣ ቀጥለው ይዘልፉሃል፣ ከዚያም ይፋለሙሃል፣ በመጨረሻም ትረታቸዋለህ::” 

“First they ignore you, then they ridicule you, then they fight you, then you win”

ማህተማ ጋንዲ (Mahatma Gandhi) 

ይንቁ የነበር እየተሳለቁ፣ ንቀታቸው ሲናቅ ስለሚጨነቁ

እንደሚመቱበት በርግጥ እያወቁ፣ ዱላ ያነሳሉ ባነሱት ሊወቁ፡፡

የሱዳን ጦር ጦቢያን ሲወር፣ የጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ጦር የታንክ ሰልፍ አላሳየም፡፡ ወያኔ ሰሜን እዝን ሲጨፍጭፍ፣ የጭራቅ አሕመድ ኦነጋዊ ጦር የታንክ ሰልፍ አላሳየም፡፡  ከወያኔ ጋር ታርቄያልሁ፣ ከሱዳንም ጋር ልታረቅ ነው በሚልበት ባሁኑ ጊዜ ግን፣ ጭራቅ አሕመድ ያሉ የሌሉ ታንኮቹን በማዥጎድጎድ ጥንካሬውን ለማሳየት እየጣረ ነው፡፡  ለምን? 

ለምን ቢሉማ ጭራቅ አሕመድ ሰብሬዋለሁ እያለ ይንቀውና ይዘልፈው የነበረው ያማራ ሕዝብ፣ ሊፋለመው እየመጣበት መሆኑን  በግልጽ ስለተረዳ ነዋ!  የመናቅ ጊዜ አልፏል፡፡  የዘለፋም ጊዜ አልፏል፡፡  ጊዜው የፍልሚያ ጊዜ ነው፡፡ ፍልሚያው ደግሞ ከፍተኛ መስዋዕትነት የሚጠይቅ ቢሆንም፣ የሚደመደመው ግን ያለ ምንም ጥርጥር በጭራቅ አሕመድ ሽንፈት ነው፡፡  ይህ ደግሞ ታሪክ ደጋግሞ የመሰከረው ታሪካዊ ሕቅ ነው፡፡  ማህተማ ጋንዲ የጠቀሰውም ይህንኑ ታሪካዊ ሐቅ ነው፡፡

ጥያቄው አማራን ለማጥፋት ቆርጦ የተነሳው ጭራቅ አሕመድ ባማራ ይሸነፋል አይሸነፍም ሳይሆን፣ አማራ እጅ ሲወድቅ ዕጣው ምን ይሆናል የሚለው ነው፡፡  እንደኔ ከሆነ ደግሞ አማሮችን ባደባባይ አስረሽኖ ዝቅዝቆ ያስሰቀለው ኦነጋዊው አውሬ ጭራቅ አሕመድ በተራው የጁን አግኝቶ የቤኒቶ ሞሶሎኒን (Benito Mussolini)፣ ጭራቁ አማሮችን በበላ ቁጥር በመዝሙር የምታበርታታው፣ ጎንደርን ካማራ ነጥላ አማራን ለማዳከም የበኩሏን የምትጣጣርው ዝናሽ ታያቸው ደግሞ የክላራ ፒታችን (Clara Petacci) ጽዋ መቅመስ አለባቸው፡፡  

መስፍን አረጋ     

mesfin.arega@gmail.com

Filed in: Amharic