ታላቁ አርበኛ ኮሎኔል ታደሠ እሸቱ እና ጓዶቻቸው የከፈሉት የሕይወት መስዋዕትነት ትግላችንን ይበልጥ ያጠናክረዋል
ኮሎኔል ታደሰ እሸቴ በውትድርና ሙያቸው አንቱ የተባሉ፣ በተለይም የውጊያ ስልጠና፣ ኢንዶክትሪኔሽን፣ አደረጃጀት፣ የሰው ኃይል ስምሪት፣ ሎጀስቲክስ፣ቅኝት፣ ተልዕኮ፣ ግዳጅ አፈጻጸም፣ ወታደራዊ ግምገማ፣ መልሶ ማደራጀት፣ የጦር ምህንድስና፣ የግንባር ውጊያ፣ የአንገት ቦታ ቁጥጥር፣ ገዥ መሬትን ቀድሞ መያዝ፣ ምሽግ ሰበራ በልዩ ሁኔታ የተካኑባቸው ወታደራዊ የሕይወት ገጻቸው ስለመሆኑ አብረዋቸው የታገሉ የትግል ጓዶቻው ብቻ ሳይሆኑ ጠላትም ጭምር የሚመሰክርላቸው ነበሩ።
ታላቁ የጦር ሰው በዓድዋ ድል መታሰቢያ ዋዜማ ለአማራነት ክብር፤ ለኢትዮጵያ ዘላቂ አንድነት በክብር ተሰውተዋል፡፡
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
ድል ለአማራ ፋኖ እና ድርጅቱ አፋህድ!