” ሁሉን አቀፍ ነፃ ፍትሃዊና ተቀባይነት ያለው ምርጫ እንዲካሄድኦፌኮ ጠየቀ…!!!

” ሁሉን አቀፍ ነፃ ፍትሃዊና ተቀባይነት ያለው ምርጫ እንዲካሄድ ኦፌኮ ጠየቀ…!!!


*…ከቀናት በፊት ሰኔ 14/2013 ዓ.ም በተደረገው ስድስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ያልተሳተፈው የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ በአንድ ዓመት ውስጥ ሁሉን አቀፍ ምርጫ እንዲደረግ ባወጣው መግለጫ ጠየቀ።
 
ፓርቲው ለአገሪቱ የፖለቲካ ኃይሎች በሙሉ የመፍትሔ ሃሳብ ብሎ የሰነዘራቸውን ሦስት ነጥቦችንም ዘርዝሯል።
በመጀመሪያ ደረጃ ሁሉን አካታች የጋራ መንግሥት እንዲቋቋምና “ያልተሳካ” ብሎ የጠራውን የመንግሥት ተሃድሶ እንዲቀጥል፣ “ሁሉን አካታች ብሔራዊ የመግባባት ድርድር እንዲጀመር” የሚሉ ሃሳቦችን አስፍሯል።
በሦስተኛነትም የጋራ መንግሥቱ በጋራ የሚፈጥር ፍኖተ ካርታ እንዲመቻችና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ሁሉን አቀፍ ነፃ ፍትሃዊና ተቀባይነት ያለው ምርጫ እንዲካሄድም የሚሉ ሃሳቦችን አቅርቧል። https://bbc.in/3qp60nZ

LEAVE A REPLY

Please enter your comment!
Please enter your name here

This site uses Akismet to reduce spam. Learn how your comment data is processed.