![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/09/FB_IMG_1600436988985-300x300.jpg)
የአማራ ነፍስ ዋጋው ስንት ነው…???
![](https://www.ethioreference.com/wp-content/uploads/2020/09/FB_IMG_1600436988985-300x300.jpg)
አሳዬ ደርቤ
ሳምንቱን ሙሉ በተናጠል የምንፈልገውንና ከሌሎች የሚሰጠንን አጀንዳ ማንጸባረቁ እንደተጠበቀ ሆኖ ለየት ባለ መልኩ ደግሞ በየትኛውም ተባራሪ አጀንዳ ሳንጠለፍ የህዝባችንን ጥያቄዎች ይዘን በጋራ የምንዘምትበት ቀን ሊኖረን እንደሚገባ ተስማምተናል፡፡ ስለሆነም፡-
.
➛ያለአግባብ ለታሰሩ ወንድሞቻችን ፍትሕን የምንጠይቅበት
➛ደብዛቸው ለጠፋ እኅቶቻችንን ድምጻችንን የምናሰማበት
➛በየስፍራው የተጨፈጨፉ ወገኖቻችንን የምናስብበት
➛የብአዴን እድሜ ጠገብ እንቦጮች ተነቃቅለው ለወገናቸው የሚያስቡ አመራሮች ወደፊት እንዲመጡ የምንታገልበት
➛በጎጥና በሃይማኖት ሊከፋፍሉን ለሚሞክሩ ሃይሎች ሕብረታችንን የምናሳይበት
➛በወገኖቻችን ላይ የተፈጸመው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ በስሙ ይጠራ ዘንድ የምንሟገትበት
➛ግፈኞች የፈጸሙብንን በደል ለሌላው ኢትዮጵያዊ የምናሳውቅበት
➛በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የሃይል ጥቃትና ኢኮኖሚያዊ መገለል እንዲቆም የምንጠይቅበት
➛የተፈናቀሉ ወገኖቻችን ይቋቋሙ ዘንድ የግላችንን ጥረት የምናደርግበበት
➛በክልላችን ችግሮችና የመፍትሔ ሐሳቦች ዙሪያ የምንመክርበት
➛የተሻለ ወቅትና ሥርዓት በትግላችን እስኪመጣ ድረስ የሚከማች በደል እንጂ የምንረሳው ግፍ አለመኖሩን የምናሳይበት
➛የአማራ ሕዝብ መሠረታዊ ጥያቄዎች እንዲመለሱ ድምጻችንን የምናሰማበት…. የሶሻል ሚዲያ የዘመቻ ቀን ‹‹ዘወትር ቅዳሜ›› እንዲሆን ተወስኗል፡፡
.